የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚያካሂደውን ሕዝበ ውሣኔ ለማስፈጸም የተመለመሉ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎችን ለሚያሠለጥኑ የመሥክ አሠልጣኞች ኅዳር 27-29 ቀን 2015 ዓ.ም. ሥልጠና ሰጠ
በቦርዱ የስልጠና ስራ ክፍል ለ299 የመሥክ አሠልጣኞች በሁለት ዙር የተሰጠው ሥልጠና በአርባ ምንጭ ከተማ የተካሄደ ሲሆን፤ ሥልጠናውም በሕዝበ ውሣኔው የመራጮች ምዝገባ ሂደት የተለያዩ ደረጃዎች ላይ የሚከናወኑ ተግባራትና ጥቅም ላይ የሚውሉ ቁሳቁሶችን የተመለከተ የንደፈ ሃሳብና የተግባር ልምምድ አካቷል።