የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ላይ ያሳለፈውን የመሠረዝ ውሣኔ አነሣ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄን (ጉሕዴን) በዐዋጅ 1162/2011 እና ይህንኑ ዐዋጅ ተግባራዊ ለማድረግ ቦርዱ ባወጣው መመሪያ ቁጥር ሦስት መሠረት በዳግም ምዝገባ ሂደት ውስጥ ማለፍ ከነበረባቸው ፓርቲዎች መካከል አንዱ ስለነበር፤ ፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔ በማድረግ መተዳደሪያ ደንቡን አሻሽሎ እንዲያቀርብ በወቅቱ መመሪያ ተሰጥቶ ነበር፡፡ ይሁንና ፓርቲው ለዳግም ምዝገባ የሚያበቃውን ሕጋዊ ቅድመ ሁኔታ በወቅቱ ባለማሟላቱ ከምዝገባ እንዲሠረዝ ቦርዱ ወሠነ፡፡