የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ክልል የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ ከአስተዳደር እና ጸጥታ አካላት ጋር ምክክር አካሄደ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙት የጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ጌዲዮ፣ ኮንሶና፣ ደቡብ ኦሞ ዞኖች እንዲሁም የቡርጂ፣ አማሮ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ እና አሌ ልዩ ወረዳዎች የሚያካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ ጥቅምት 7 ቀን 2015 ዓ.ም ከአስተዳደር እና ጸጥታ አካለት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ፡፡
በምክክር መድረኩ የሕዝብ ውሣኔው አጠቃላይ ዕቅድና አፈጻጸሙን በተመለከተ ገለጻ ተደርጓል። የህዝበ ውሳኔውን ሰላማዊነት ከማረጋጋጥ እና ከሎጅስቲክስ አንፃር የክልሉ እና የአካባቢ አስተዳደር መዋቅሮች ያለባቸው ሀላፊነት በተመለከተም ማብራሪያ ተሰጥቷል።