Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲን በተመለከተ ከቦርዱ የተሰጠ መግለጫ

የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ ሊቀመንበር ከሀገር መውጣታቸውንና ፓርቲውንም የሚመራ ሰው መወከላቸውን ከውጭ ሀገር ሆነው ለቦርዱ ሲያሳውቁ ከፓርቲው አመራሮች መኃል ይህ በሊቀመንበሩ የተሰጠው የውክልና ሥልጣን ደንቡን የተፃረረ ነው የሚል ቅሬታ ለቦርዱ አቀረቡ፡፡ ቦርዱም ሊቀመንበሩ የሰጡት የውክልና ሥልጣን ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ አንፃር የተፈፀመ መሆን አለመሆኑን መረመረ፡፡ የፓርቲው መተዳደያ ደንብ አንቀጽ 22/1/ የፓርቲው ሊቀመንበር በማይኖሩበት ወቅት ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበሩ ሊቀመንበሩን ተክተው እንደሚሰሩ ደንግጓል፡፡ በዚሁ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ከሀገር በወጡት የፓርቲው ሊቀመንበር የተሰጠው ውክልና ደንቡን የተፃረረ በመሆኑ ቦርዱ ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡ በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀጽ 22/1/ መሠረትም እንዲፈፅም ወስኗል፡፡ ይሁንና በፓርቲው አመራሮች መኃል አለመግባባቱ እየጨመረ በመሄዱ በአዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 74 (6) መሠረት ጉዳያቸው በባለሙያዎች ጉባኤ እንዲታይ ቦርዱ ወስኖ የባለሙ

Share this post

የ6ኛው ዙር ቀሪና ድጋሚ ምርጫ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በመስቃንና ማረቆ የምርጫ ክልል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. እንዲሁም መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች ምርጫው ባልተካሄደባቸው እንዲሁም ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸው በአፋር፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ምርጫዎችን ያካሂዳል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በመስቃንና ማረቆ የምርጫ ክልል ለሚደረገው ድጋሚ ምርጫ:

- በቀበሌ 1 ምርጫ ጣቢያ ቆሼ

- በሰሜን ቆሼ ምርጫ ጣቢያ ቁጥር 1

- በቆሼ 02 ምርጫ ጣቢያ ቁጥር 3 እንዲሁም

-በእንሴኖ 01 ምርጫ ጣቢያ ቁጥር 2 የመራጮች ምዝገባ ከሚያዝያ 21 እስከ ግንቦት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ ይከናወናል።

የ6ኛው ዙር ቀሪና ድጋሚ ምርጫ በአፋር ክልል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. እንዲሁም መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች ምርጫው ባልተካሄደባቸው እንዲሁም ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸው በአፋር፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ምርጫዎችን ያካሂዳል።

በአፋር ክልል ለሚካሄደው ምርጫ በዳሎል፥ ጉሊና፥ አዲሌላ፥ ዳሊፋጌ፥ እንዲሁም ዳዌ የምርጫ ክልሎች በሙሉ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ የሚከናወን ሲሆን:

የ6ኛው ዙር ቀሪና ድጋሚ ምርጫ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. እንዲሁም መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች ምርጫው ባልተካሄደባቸው እንዲሁም ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸው በአፋር፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ምርጫዎችን ያካሂዳል።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለሚካሄደው ምርጫ በ ደምቤ፥ ምዥጋ፥ ሰዳል፥ ዛይ፥ ቡለን፥ ዳንጉር፥ ድባጤ፥ ወንበራ፥ ማንዱራ፥ ፓዌ፥ ጉባ፥ እና ልዩ ሽናሻ የምርጫ ክልሎች በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ በሙሉ የሚከናወን ሲሆን ፡

• በመንጌ የምርጫ ክልል፤ በሰላማ ምርጫ ጣቢያ ሰላማ-ሀ

• በሆሞሻ የምርጫ ክልል፤ በ01 ቀበሌ ምርጫ ጣቢያ 01 ቀበሌ 01 ሀ2B

• በአሶሳ ሆሃ ምርጫ ጣቢያ፤ አምባ 7 ምርጫ ጣቢያ አምባ 7

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛዉ ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸዉ የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማእከላዊ ኢትዮጵያ በሚገኙ ምርጫ ክልሎች ምርጫ ለማከናወን የወጣ የምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሰሌዳ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛዉ ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸዉ የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማእከላዊ ኢትዮጵያ በሚገኙ ምርጫ ክልሎች ምርጫ ለማከናወን የወጣ የምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሰሌዳ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫና በድኅረ ምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን በተመለከተ አስጠንቶ ባጠናቀቀው ጥናት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫ እና በድህረ ምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን በተመለከተ አስጠንቶ ባጠናቀቀው ጥናት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር መጋቢት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. ውይይት አካሄደ። ከጥናቱ መጠናቀቅ አስቀድሞ ፤ላለፉት ወራት ጥናቱን መሠረት ያደረጉ ውይይቶች ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ያካሄደ ሲሆን፤ በዚሁ በተጠናቀቀው ጥናት ላይ መጋቢት 12 በተደረገው ውይይት ደግሞ ከዚህ በፊት ያልተሳተፉ ግን የሚመለከታቸው ሲቪል ማኅበራትን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ባዘጋጀው የሴቶች እና የአካል ጉዳተኞች ሩጫ ላይ ተሳትፎ አደረገ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እሁድ መጋቢት 8 ቀን 2016 ዓ.ም. በተካሄደው የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የሴቶችና እና የአካል ጉዳተኞች ሩጫ ላይ ተሳትፎ ያደረገ ሲሆን በተለይ የአካል ጉዳተኞች ውድድር ላይ ትኩረት በማድረግ ለአባላቱ ያለውን አጋርነት አጠናክሯል። በዕለቱ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ጀምሮ እስከ ሁለት ተኩል የቀጠለው የሴት አካል ጉዳተኞች የሩጫ ውድድር ‘የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአካል ጉዳተኞች ውድድር' በሚል ስያሜ የተካሄደ ሲሆን በውድድሩ ላይ ከተለያዩ በአካል ጉዳተኞች ጉዳይ ላይ ከሚሠሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አባላት የተውጣጡ ሴት የአካል ጉዳተኞች ተሳትፈዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለአንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ያሳለፈዉ ዉሳኔ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ ‘አንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ’ በ 2015 ዓ.ም በቦርዱ የተደረገለትን የበጀት ድጋፍ ለታለመለት ዓላማ እንዳላዋለ እና ከፍተኛ ገንዘብ በፓርቲው አመራሮች እና ሌሎች አባላት ለግል ጥቅም እንዲውል መደረጉን በመገንዘቡ ፓርቲው እና አመራሮቹ እንዲታገዱ፤ተገቢው የወንጀል ምርመራ እንዲጀመር እና አላግባብ ወጪ የሆነውን ገንዘብ በተመለከተ የፍ/ብሄር ክስ እንዲመሰረትና ገንዘቡ ለቦርዱ ተመላሽ እንዲደረግ የካቲት 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ውሳኔ አሳልፋል፡፡

ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post