Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የሳልሳይ ወያነ ትግራይ ፓርቲ አደራጅ ኮሚቴ ዐዋጁን መሠረት በማድረግ የመሥራች ጉባዔውን እንዲያከናውን መወሠኑን ያሳወቀበት ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የሳልሳይ ወያነ ትግራይ ፓርቲ አደራጅ ኮሚቴ ዐዋጁን መሠረት በማድረግ የመሥራች ጉባዔውን እንዲያከናውን መወሠኑን ያሳወቀበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በዎላይታ ዞን የድጋሚ ህዝብ ውሳኔ ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እያከናወነ ነው።

በዚሁ መሠረት በዎላይታ ዞን ስር በሚገኙ ምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ ህዝበ ውሳኔ የሚያስፈጽሙ ሠራተኞችን በጊዜያዊነት ለመቅጠር ይፈልጋል። በመሆኑም የዎላይታ አካባቢ ነዋሪ የሆናችሁ፣ በምርጫ አስፈጻሚነት በገለልተኝነት ማገልገል የምትፈልጉ እና ከፓርቲ አባልነት ነፃ የሆናችሁ አመልካቾች ከግንቦት 3 እስከ ግንቦት 10 ቀን 2015 ዓ.ም ብቻ እንድታመለከቱ ቦርዱ ያሳውቃል።

የምልመላ መሥፈርት፡-

• ዕድሜው/ዋ ከ18 ዓመት በላይ የሆነ/ች፣

• የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ/ች፣

• የትምህርት ዝግጅት፦12ኛ ክፍል ያጠናቀቀ/ች እና ከዚያ በላይ የሆነ/ች፣

• የሥራ ቦታ፦ በዎላይታ ዞን ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ቀበሌ እና ምርጫ ጣቢያዎች፣

• የስራ ቆይታ ፦ ከ8 እስከ 10 ቀን

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን የሚካሄደውን የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔን ምርጫ በተመለከተ ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና ከኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ጋር ምክክር አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን የሚደረገውን የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ ምርጫ አስመልክቶ በመራጮች ትምህርትና በምርጫ መታዘብ ላይ ከተሠማሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እንዲሁም በሰብዓዊ መብት ክትትል ተግባራት ላይ ከተሠማራው ከኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጋር ሚያዚያ 26 ቀን 2015 ዓ.ም. ውይይት አካሄደ። የውይይት መድረኩ የቦርድ አመራር አባል የሆኑት ብዙወርቅ ከተተ ባደረጉት ንግግር የተከፈተ ሲሆን፤ በንግግራቸውም የድጋሚ ምርጫ ማካሄድ ያስፈለገበት ዋና ዋና ምክንያቶች አብራርተዋል። በተጨማሪም የመራጮች ትምህርት በሚሰጥበት ወቅት ምን ምን ጉዳዮች መካተት እንዳለባቸው እና ልዩ ድጋፍ የሚሹ የማኅበረሰቡን ክፍሎች ተደራሽ ሊደረጉ የሚችሉበትን አግባብነትና አማራጮች አስረድተዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልል በሚገኘው የዎላይታ ዞን ላይ የሚያካሄደው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ የትግበራ አፈጻጸም ዝርዝር ዕቅድ ማሳያ ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልል በሚገኘው የዎላይታ ዞን ላይ የሚያካሄደው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ የትግበራ አፈጻጸም ዝርዝር ዕቅድ ማሳያ ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳ

wolita election time table

 

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን የሚደረገውን የድጋሜ የሕዝበ ውሣኔ ምርጫ አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን የሚደረገውን የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ ምርጫ አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትላንትናው ዕለት ሚያዚያ 26 ቀን 2015 ዓ.ም. ውይይት አካሄደ። የፌዴሬሽን ምክር ቤትና የሕዝብ ተወካዩች ቋሚ ኮሚቴ ተወካዩች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች፣ የዞኑ አመራሮችና የፀጥታ አካላት እንዲሁም የፌደራል ፖሊስና የፍትሕ ሚኒስቴር ተወካዮች የተገኙበትን መድረክ በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም የመድረኩ ዋና ዐላማ በወላይታ ዞን የተደረገው ሕዝበ ውሣኔ ላይ ቀደም ሲል ያጋጠሙ የሕግ ጥሠቶች በድጋሚ እንዳይፈጠሩ አስቻይ ሁኔታዎችን በጋራ ለመፍጠር ታሳቢ እንዳደረገና ይህንንም ለማድረግ የመድረኩ ተሣታፊ የሆኑት ባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ እንደሆነ በማሰብ ጭምር እንደሆነ ተናግረዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (በኮንሶ፣ በደቡብ ኦሞ፣ በወላይታ፣ በጋሞ፣ በጌዴኦ፣ በጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (በቡርጂ፣ በባስኬቶ፣ በአሌ፣ በአማሮ፣ በዲራሼ) ያካሄደውን የሕዝበ ውሣኔ ውጤት ስለማሳወቅ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (በኮንሶ፣ በደቡብ ኦሞ፣ በወላይታ፣ በጋሞ፣ በጌዴኦ፣ በጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (በቡርጂ፣ በባስኬቶ፣ በአሌ፣ በአማሮ፣ በዲራሼ) ላይ ያካሄደውን የሕዝበ ውሣኔ ጊዜያዊ ውጤት የማዳመር ሥራ በሁሉም ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ላይ አጠናቆ በዞንና በልዩ ወረዳ ደረጃ ጊዜያዊ ውጤቶች ይፋ ተደርገዋል።

Share this post

ቦርዱ የሚያካሂደውን የሕዝበ ውሣኔው ጊዜያዊ ውጤት የማጣራትና የማረጋገጥ ሥራ እንድትታዘቡ ጥሪ ስለማቅረብ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (በኮንሶ፣ በደቡብ ኦሞ፣ በወላይታ፣ በጋሞ፣ በጌዴኦ፣ በጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (በቡርጂ፣ በባስኬቶ፣ በአሌ፣ በአማሮ፣ በዲራሼ) ላይ ያካሄደውን የሕዝበ ውሣኔ ጊዜያዊ ውጤት የማመሳከር ሥራ በሁሉም ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ላይ አጠናቆ በዞንና በልዩ ወረዳ ደረጃ ጊዜያዊ ውጤቶችን ለሕዝብ ይፋ አድርጓል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሕዝበ ውሣኔውን ጊዜያዊ ውጤት ይፋ ማድረግ ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (በኮንሶ፣ በደቡብ ኦሞ፣ በወላይታ፣ በጋሞ፣ በጌዴኦ፣ በጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (በቡርጂ፣ በባስኬቶ፣ በአሌ፣ በአማሮ፣ በዲራሼ) ላይ ያካሄደው የሕዝበ ውሣኔ ድምፅ የመስጠት ሂደት መጠናቀቁን ተከትሎ፤ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ ውጤት የማዳመር ሥራው ድምፅ በተሰጠባቸው ጣቢያዎች የተከናወነ ሲሆን፤ ውጤቱም ጥር 30 ቀን 2015 ከጠዋት ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያዎች ለሕዝብ ይፋ ተደርጓል።

የተዳመረና የተመሳከረ ጊዜያዊ ውጤት በልዩ ወረዳ ደረጃ ይፋ ከተደረገባቸው ውስጥ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ እና ባስኬቶ ሲጠቀሱ፤ በዞን ደረጃ ደ’ሞ በኮንሶ ይፋ ተደርጓል። በተጠቀሱት ቦታዎች የጊዜያዊ ውጤቱ የማዳመርና ማመሳከር ሥራው ከጥር 30 ቀን 2015 ዓ.ም. እስከ የካቲት 1 ቀን 2015 ዓ.ም. ባለው ጊዜ የተሠራ ነው።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች ዲራሼ) ላይ እያካሄደ ባለው የሕዝበ ውሣኔ ሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው መራጮች ድምጽ በመስጠት ላይ ይገኛሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ወላይታ፣ ጋሞ ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ እያካሄደ ባለው የሕዝበ ውሣኔ ሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው መራጮች ድምጽ በመስጠት ላይ ይገኛሉ

ቦርዱ በተለያዩ የመርጫ ጣቢያዎች ላይ እያደረገ ባለው ክትትል መሰረት የደረሰባቸው ግኝቶች እና የወሰዳቸው እርምጃዎች ከስር ተዘርዝረዋል

• 9 የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የተለያዩ የምርጫ ቁሳቁስ ጉድለት ሪፓርት የተደረገ ሲሆን ይህንኑ ለመቅረፍ በምርጫ ማእከል ደረጃ የማስተካከያ እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል

Share this post