Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ለሚያካሂደው የሕዝበ ውሣኔ የመራጮች ድምጽ የመስጠት ሂደት እየተካሄደ ይገኛል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ወላይታ፣ ጋሞ ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ ለሚያካሂደው የሕዝበ ውሣኔ የመራጮች ድምጽ የመስጠት ሂደት እየተካሄደ ይገኛል፡፡

Share this post

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በነገው’ለት ጥር 29 ቀን 2015 ዓ. ም. በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ለሚያካሂደው የሕዝበ ውሣኔው በድምፅ መስጫ ቀን አገልግሎት ላይ የሚውሉ ቁሳቁሶችን በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች አሠራጭቶ አጠናቀቀ

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በነገው’ለት ጥር 29 ቀን 2015 ዓ. ም. በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ወላይታ፣ ጋሞ ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ ለሚያካሂደው የሕዝበ ውሣኔው በድምፅ መስጫ ቀን አገልግሎት ላይ የሚውሉ ቁሳቁሶችን በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች አሠራጭቶ አጠናቀቀ።

Share this post

የቡሌ ምርጫ ክልል ድጋሚ ምርጫን ይመለከታል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ወላይታ፣ ጋሞ ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ ከሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ ጎን ለጎን በቡሌ ምርጫ ክልል ላይ የድጋሚ ምርጫ እንዲካሄድ በወሠነው መሠረት ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. ምርጫው በጋራ እንደሚካሄድ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተለያዩ ምክንያቶች እንዲደገም ውሣኔ በተላለፈባቸው ምርጫ ክልሎች ላይ በዚህ ዓመት ምርጫውን ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እያከናወነ ይገኛል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተለያዩ ምክንያቶች እንዲደገም ውሣኔ በተላለፈባቸው ምርጫ ክልሎች ላይ በዚህ ዓመት ምርጫውን ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እያከናወነ ይገኛል።

በዚሁ መሠረት በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት ሥር በምቃንና ማረቆ ሁለት ምርጫ ክልል፣ በአፋር ክልል ደሉል ምርጫ ክልል እንዲሁም በቤኒሻንጉል ክልል መንጌ ምርጫ ክልል ላይ ለሚያካሂደው የድጋሚ ምርጫ፤ ምርጫውን የሚያስፈጽሙ ሠራተኞችን በጊዚያዊነት ለመቅጠር ይፈልጋል። ስለሆነም በተጠቁሱት አካባቢዎች ውስጥ የምትኖሩ በምርጫ አስፈጻሚነት በገለልተኝነት ማገልገል የምትፈልጉ እና ከፓርቲ አባልነት ነፃ የሆናችሁ አመልካቾች ከጥር 19 እስከ የካቲት 3 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ እንድታመለከቱ ቦርዱ ያሳውቃል።

የምልመላ መሥፈርት፡‐

• ዕድሜው/ዋ ከ18 ዓመት በላይ የሆነ/ች፣

• የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ/ች፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያካሄደው የመራጮች ምዝገባ አጠቃላይ አኅዛዊ መረጃ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ወላይታ፣ ጋሞ ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ በ3769 ምርጫ ጣቢያዎች ባካሄደው የመራጮች ምዝገባ ባጠቃላይ 3,028,770 የመራጮች ቁጥር የተመዘገበ ሲሆን፤ ከነዚህም ውስጥ 493 የአካል ጉዳተኞች ይገኙበታል።

አጠቃላይ የተመዝጋቢው ቁጥር በፆታ ሲገለጽ 1,575,371 ወንዶች ሲሆኑ ቀሪ 1,453,399 ሴቶች ናቸው። ከተመዘገቡት የአካል ጉዳተኞች ውስጥም እንዲሁ 296 ወንዶች ሲሆኑ ቀሪ 197 ሴቶች ናቸው። ከላይ የተመለከቱት አኅዞች ቀደም ሲል ቦርዱ ይፋ ባደረገው ጊዜያዊ የመራጮች ቁጥር ላይ ባለመጠናቀቃቸው ያልተካተቱትን ጣቢያዎች እንዲሁም የድጋሚ ቆጠራ የተደረገባቸውን ጣቢያዎች ጭምር የያዘ ሲሆን፤ ድምር ውጤቱም በማዕከል ደረጃ የመጨረሻ የሚባለው የማረጋገጥ ሥራ የተከናወነበት ነው።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ አስመልክቶ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የሕዝበ ውሣኔው ምርጫ አስፈጻሚዎችን ለሚያሠለጥኑ ባለሞያዎች ሥልጠና መሰጠት ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ዎላይታ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት የውጤት ማመሳከር፣ የማዳመርና ይፋ የማድረግ ሂደትን አስመልክቶ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የሕዝበ ውሣኔው ምርጫ አስፈጻሚዎችን ለሚያሠለጥኑ ባለሞያዎች ሥልጠና መሰጠት ጀመረ። በዚህ መሠረት እስካሁን የሚከተሉት ሥልጠናዎች ተሰጥተዋል፦

- በሕዝበ ውሣኔ የድምፅ መስጫ ቀን የውጤት ማመሳከርና የማዳመር ሥልጠና ለመሪ አሠልጣኞች እና ለተወሠኑ የቦርዱ ኦፕሬሽን ክፍል ባልደረባዎች ጥር 4 እና ጥር 5 ቀን 2015 ዓ.ም. እንዲሁም ጥር 8 እና ጥር 9 ቀን 2015 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተሰጥቷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ታኅሣሥ 19 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ (ኢ. ብ. አ. ፓ) ነሐሴ 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ በሚመለከት ቦርዱ ያሳለፈዉ ዉሳኔ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ታኅሣሥ 19 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ (ኢ. ብ. አ. ፓ) ነሐሴ 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ በሚመለከት ፓርቲው ከሪፖርት ጋር አያይዞ ያቀረባቸውን ሠነዶች ከሕጉ፣ ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ እና የቦርዱ ታዛቢዎች ካቀረቡት ሪፖርት አንጻር መርምሮ ውሣኔ አሣልፏል።

ቦርዱ ባደረገው ምርመራ ፓርቲው ያካሄደው ጠቅላላ ጉባዔ ያሻሻለው የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ ግልጽ ያልሆኑ፣ መካተት ኖሮባቸው ያልተካተቱ አንቀጾችን የለየ ሲሆን፣ ከዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 ጋር የሚቃረኑ አንቀጾች ተፈጻሚ እንዳይሆኑና ጠቅላላ ጉባዔው በቀጣይ ስብሰባው አስፈላጊውን ማስተካከያ አድርጎባቸው ሪፖርት እንዲያቀርብ ቦርዱ ወሥኗል። ከላይ የተጠየቁ ማስተካከያዎች እንደተጠበቁ ሆነው ፓርቲው ነሐሴ 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ እና የተላለፉ ውሣኔዎችን ቦርዱ የመዘገበ መሆኑን ለፓርቲው በላከው ደብዳቤ አሳውቋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ የተለያዩ የዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ዎላይታ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ የተለያዩ የዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል።

የቦርዱ የሎጅስቲክ ሥራ ክፍል ለሕዝበ ዉሣኔው ድምፅ መስጫ ቀን የሚያገለግሉ የተለያዩ ሠነዶችና ቁሳቁሶችን (መጠባበቂያን ጨምሮ) ለ3,769 ምርጫ ጣቢያዎች ለሥርጭት ዝግጁ በሆነ መልኩ የማሸግ ሥራውን አጠናቋል። በእሽጉ ውስጥ ከተካተቱ ሠነዶች እና ቁሳቁሶች መካከል የድምፅ መስጫ ወረቀቶች፣ የሕዝበ ዉሣኔው ውጤት ማመሳከሪያ እና ማሳወቂያ እንዲሁም በድምፅ መስጫ ቀን ጥቅም ላይ የሚውሉ ሌሎች አስፈላጊ ሠነዶች ይገኙበታል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የኢትዮጵያ ነጻነት ፓርቲ (ኢ. ነ. ፓ) ሚያዝያ 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ በሚመለከት ቦርዱ ያሳለፈዉ ዉሳኔ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የኢትዮጵያ ነጻነት ፓርቲ (ኢ. ነ. ፓ) ሚያዝያ 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ በሚመለከት ፓርቲው ከሪፖርት ጋር አያይዞ ያቀረባቸውን ሠነዶች ከሕጉ፣ ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ እና የቦርዱ ታዛቢዎች ካቀረቡት ሪፖርት አንጻር መርምሮ ውሣኔ አሣልፏል።

Share this post

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተለያዩ ምክንያቶች ባልተካሄደባቸው የተወሠኑ ምርጫ ክልሎች ላይ ለሚያካሄደው ምርጫ፤ ምርጫ አስፈጻሚ ሠራተኞችን በጊዚያዊነት ለመቅጠር ይፈልጋል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተለያዩ ምክንያቶች ባልተካሄደባቸው የተወሠኑ ምርጫ ክልሎች ላይ በተያዘው ዓመት ምርጫውን ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ተግባራት በማድረግ ላይ መሆኑ ይታወቃል።

በዚሁ መሠረት በአማራ ክልል በሮቢት፣ በኤፌሶን፣ በማጀቴ፣ በሞላሌ እና በአርጎባ ልዩ ምርጫ ክልሎች ለሚያካሄደው ምርጫ፤ ምርጫ የሚያስፈጽሙ ሠራተኞችን በጊዚያዊነት ለመቅጠር ይፈልጋል። በዚሁ መሠረት በተጠቁሱት አካባቢዎች ውስጥ የምትኖሩ በምርጫ አስፈጻሚነት በገለልተኝነት ማገልገል የምትፈልጉ እና ከፓርቲ አባልነት ነፃ የሆናችሁ ከጥር 8 እስከ ጥር 15 ቀን 2015 ዓ.ም እንድታመለከቱ ቦርዱ ይጠይቃል።

የምልመላ መሥፈርት፡-

• ዕድሜው/ዋ ከ18 ዓመት በላይ የሆነ/ች፣

• የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ/ች፣

• መኖሪያ አድራሻ፦ በምርጫ ክልሉ ውስጥ በሚገኙ ቀበሌ ውስጥ የሆነ/ች፣