የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሕዝበ ውሣኔ በሚካሄድባቸው አንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች ላይ የተፈጸሙ የሕግ ጥሠቶችን በተመለከተ የወሰዳቸው የዕርምት ዕርምጃዎች
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደ/ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ለሚያከሂደው ሕዝበ ውሣኔ የምርጫ ጣቢያዎችን በማቋቋም የመራጮች ምዝገባ እያከናወነ እንደሚገኝ ይታወቃል። ይህንንም የምዝገባ ሂደት ለመከታተትልና ለመቆጣጠር ከቦርዱ የኦፕሬሽን ሥራ ክፍል የተዋቀረ ቡድን ከታኅሣሥ 16 - ታኅሣሥ 18 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ ባደረገው የክትትል ሥራ፤ በዎላይታ እና በጎፋ ዞኖች በሚገኙ ከታች በዝርዝሩ ላይ በተጠቀሱት የምርጫ ጣቢያዎች ላይ መሠረታዊ የሆኑ የሕግ ጥሠቶች መፈጸማቸውን አረጋግጧል።