የሕዝበ ውሳኔው ጥያቄ እና ምልክቶች ስለማሳወቅ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ቱ ዞኖች (ኮንሶ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና በ5ቱ ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ህዝበ ውሳኔ ለማካሄድ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል። በዚሁ መሰረት ቦርዱ የህዝበ ውሳኔ ጥያቄ በተመለከተ ውሣኔ ሰጥቷል፡፡ ምልክቶችን የማስመረጥም ሂደት አከናውኗል፡፡
የሕዝበ ውሣኔው ጥያቄ አማራጮች፡-
1. “የ6ቱ ዞኖች (ኮንሶ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና 5ቱ ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) በአንድ የጋራ ክልል መደራጀትን እደግፋለሁ” የሚለው ነው፡፡ ለዚህ ጥያቄ ምልክት ነጭ እርግብ በአስተዳደር ምክር ቤቶቹ ተመርጧል፡፡