በአዲሱ የምርጫና የፓለቲካ ፓርቲዎች አዋጅ ላይ የተደረገው ውይይት
ሐምሌ 24 ቀን 2011 ዓ.ም.
በአዲሱ የምርጫና እና የፓለቲካ ፓርቲዎች አዋጅ ላይ የተደረገውን ውይይት አስመልክቶ የፋና ብሮድካስቲንግ ዘገባን ማየት ይችላሉ። ዘገባው የተነሱ ጥያቄዎችንና በቦርዱ ኃላፊዎችና በህግ አርቃቂ ባለሞያዎች የተሰጡትን መልሶች ያስቃኛል።
ይህ የስራ ማስታወቂያ አይደለም፡፡
ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተላለፈ ለባለሞያዎች ዝርዝር(Professionals roster) ውስጥ ማካተቻ ጥሪ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባለፉት ስድስት ወራት የተለያዩ ተቋማዊ ለውጦችን ለማካሄድ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ከነዚህም ለውጦች መካከል ዋናው ተቋሙን ከፍተኛ አቅምና ቁርጠኝነት ያለው የሰው ሃይል እንዲኖረው ጥረት ማድረግ ነው፡፡
በዚህም መሰረት የቦርዱ ጽ/ቤት በተለያዩ ሞያዎች የከፍተኛ ክህሎት ባለቤት የሆኑ ግለሰቦችን ግለታሪክ (ካሪኩለም ቪቴ) መሰብሰብና የባለሞያዎች ዝርዝር በማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖም ሲገኝ በበጎ ፍቃደኝነት፣ በጊዜያዊ ኮንትራት ስራ፣ እንዲሁም በቅጥር ከተቋሙ ጋር አብረው መስራት የሚችሉበትን መንገድ ለማመቻቸት ይፈልጋል::
ሐምሌ 24 ቀን 2011 ዓ.ም.
በአዲሱ የምርጫና እና የፓለቲካ ፓርቲዎች አዋጅ ላይ የተደረገውን ውይይት አስመልክቶ የፋና ብሮድካስቲንግ ዘገባን ማየት ይችላሉ። ዘገባው የተነሱ ጥያቄዎችንና በቦርዱ ኃላፊዎችና በህግ አርቃቂ ባለሞያዎች የተሰጡትን መልሶች ያስቃኛል።
ሐምሌ 18 ቀን 2011 ዓ.ም.
በጠቅላይ አቃቤ ህግ ስር በሚገኘው በህግና በፍትህ ማሻሻያ ምክር ቤት የዴሞክራሲ ተቋማት የሥራ ቡድን አዲሱ የምርጫና የፓለቲካ ፓርቲዎች አዋጅን ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር በመተባበርና ከተለያዩ የፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመወያየት የተረቀቀውን ህግ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማቅረቡ ይታወሳል፡፡ በትላንትናው ዕለት የዴሞክራሲና የፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለሕዝብ ክፍት የሆነ ውይይት ያዘጋጀ ሲሆን የተለያዩ የፓለቲካ ፓርቲዎችና የሲቪክ ማህበራት ተወካዮች ተሳትፈውበታል፡፡ በዚህ ውይይት የተለያዩ በህጉ ላይ የተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ የተሰጠባቸው ሲሆን ሁለት ጉዳዮች በዋናነት ሰፊ ውይይትና ክርክር ተደርጎባቸዋል፡፡ የህግ አርቃቂ ባለሞያዎቹ እና የቦርዱ ኃላፊዎችም ለጥያቄዎቹ መልስ የሰጡ ሲሆን የህጉን መነሻ መርሆዎች በዝርዝር ማብራሪያ አቅርበዋል፡፡
ሁለቱ ከፍተኛ ክርክር የተደረገባቸው ጉዳዮች;
ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተላለፈ ለባለሞያዎች ዝርዝር (Professionals roster) ውስጥ ማካተቻ ጥሪ
ሰኔ 13 ቀን 2011 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ከጣልያንዋ ምክትል የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተገናኝተው ውይይት አድርገዋል በውይይቱም ወቅት የሚቀጥለውን ምርጫ አስመልክቶ በጣልያን መንግሥት እና ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መካከል ሊኖር ስለሚችለው ትብብር ተነጋግረዋል። ሚኒስትሯ በበኩላቸው የጣልያን መንግሥት የሚቀጥለውን ምርጫ ጋር የተያያዙ ሥራዎችን ለመደገፍ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለው ገልጸዋል።
ሰኔ 13 ቀን 2011 ዓ.ም.
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ በትላንትናው ዕለት ከተባበሩት መንግሥታት የልማት ድርጅት እና ከገንዘብ ሚኒስትር ጋር በመሆን የጋራ የፕሮጄክት ሰነድ ፈርመዋል። የ40 ሚልዮን ዶላር በጀት ያለው የፕሮጄክት ሰነዱ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሚቀጥለውን አገራዊ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሃዊና ተአማኒ እንዲሆን የምርጫ ቦርድን አቅም ማሳደግን ጨምሮ ለተለያዩ ከምርጫ ጋር ግንኙነት ላላቸው ተግበራት መሳካት የሚውል ሲሆን ካናዳ፣ ዴንማርክ፣ ፊንላንድ፣ ጀርመን፣ አየርላንድ፣ ጃፓን፣ ኔዘርላንድ፣ ኒውዚላድ፣ ኖርዌይ እና ስዊድን ለበጀቱ አስተዋእጾ አድርገዋል።
ሰኔ 1 ቀን 2011 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አባላትን ለመሾም በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አማካኝነት የተቋቋመው እጩዎችን መልማይ ኮሚቴ በዛሬው ዕለት ስምንት እጩዎችን ይፋ አድርጓል። ስምንቱ እጩዎች ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ለመጨረሻ ውሳኔ የቀረቡ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በሚቀጥሉት ሳምንታት አራቱን የቦርድ አባላት ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበው ያፀድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ግንቦት 20 ቀን 2010 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ “በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የሚዲያዎች ሚና” በሚል ርዕስ ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር ምክክር አደረገ። ቦርዱ ከአውሮፓ ህብረት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የምክክር አውደጥናት ግንቦት 19 ቀን 2011 ዓ.ም. ተካሂዷል፡፡