Skip to main content

የምርጫ ቦርድ የጥሪ ማዕከል አገልግሎት መስጠት ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ባልተካሄደባቸው ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ሶማሌ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና አፋር ክልሎች ቀሪና የድጋሚ ምርጫ ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ለማከናወን በዝግጅት ላይ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም መሰረት ቦርዱ ምርጫ በሚያደርግባቸው አካባቢዎች ለሚፈጠሩ ልዩ ልዩ ሁኔታዎች እና ለመረጃ መለዋወጥ እንዲያገለግል ጊዜያዊ የጥሪ ማዕከል አቋቁማል ስለሆነም ከ6ኛው ዙር ሀገራዊ ቀሪና የድጋሚ ምርጫ ጋር በተያያዘ መረጃ ለማግኘት፤መረጃ ለመስጠት እና አስፈላጊ የሆኑ ጥቆማዎችን ለምርጫ ቦርድ ለማቅረብ የሚከተሉትን ነፃ የስልክ መስመሮች ይጠቀሙ፡

Share this post