Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

NEBE study visit in Berlin

The Board of NEBE was invited to Germany by its long-standing partner: the Netherlands Institute for Multiparty Democracy (NIMD). The study visit was in Berlin from the 15th to the 19th of April 2024.

The study visit focused on: Germany's electoral system (legal framework, institutions and management); learning about political party registration, administration/regulation; and getting an understanding of the Berlin State Election Commission's relations with other Governmental organs (Federal Parliament and Regional Parliaments)

Share this post

የእጩዎች የመጨረሻ ዙር የማጣራት ሂደት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛውን ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. እንደሚያከናውን ይታወቃል ነገር ግን ስማችሁ ከዚህ በታች የተዘረዘረው ግለሰቦች በ 2013 ዓ.ም በ6ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ወቅት እጩ የነበራችሁ ሲሆን አሁን በምናደርገው ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ እንድትሳተፉ በቦርዱ የመረጃ ቋት ውስጥ ባላችሁ ስልክ ቁጥር በመደወል ለማግኘት የተደረገው ጥረት ስልካችሁ ሊሰራ ባለመቻሉ ምክንያት ሊሳካ አልቻለም። ይሁን እንጂ ቦርዱ በምርጫ አዋጁ 1162/2011 አንቀጽ 39 (2) መሰረት የእጩዎችን የመወዳደር መብት ለመጠበቅ የመጨረሻ ማጣራት እያከናወነ ይገኛል፡፡

በዚህ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተዘረዘረው ግለሰቦች አስከ ግንቦት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. እስከ ጠዋቱ አራት ሰዓት ድረስ በስልክ ቁጥር 0995003794 በመደወል እንድታሳውቁ ቦርዱ ጥሪ ያቀርባል፡፡

Share this post

እጩ ከነበራችሁበት ፓርቲ መልቀቃችሁን ስለማሳወቅ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛውን ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. እንደሚያከናውን ይታወቃል፡፡ ለዚህም ይረዳ ዘንድ የዕጩ ምዝገባ ከሚያዝያ 21 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን ስማችሁ ከዚህ በታች የተገለጹት የፓርቲያችሁ አባላት በዚህ ምርጫ እንደማይሳተፉ እና በሌላ እጩ መተካታቸውን አሳውቃችሁናል፡፡ ይሁን እንጂ ቦርዱ በምርጫ አዋጁ 1162/2011 አንቀጽ 39 (2) መሰረት የእጩዎችን የመወዳደር መብት ለመጠበቅ የመጨረሻ ማጣራት እያከናወነ ይገኛል፡፡

በመሆኑም ግለሰቦችን በቦርዱ የመረጃ ቋት ውስጥ ባላቸው ስልክ ቁጥር በመደወል ለማግኘት የተደረገው ጥረት ስልካቸው ሊሰራ ባለመቻሉ ምክንያት ሊሳካ አልቻለም። በዚህ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተዘረዘረው ግለሰቦች ከፖለቲካ ፓርቲያችሁ መልቀቃቸሁን ለፓርቲያችሁ እንድታሳውቁ እና መልቀቃችሁን የሚገልጽ ሰነድ ለቦርዱ እንድትልኩ እንጠይቃለን።

Share this post

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ዙር የጠቅላላ እና የድጋሚ ምርጫ ባልተካሄደባቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. የሚካሄደውን ምርጫ መዘገብ ለምትፈልጉ የመገናኛ ብዙኃን የቀረበ ጥሪ

የመገናኛ ብዙኃን ቀጣዩ የ6ኛው ዙር የጠቅላላ እና የድጋሚ ምርጫ ባልተካሄደባቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ምርጫው ፍትሐዊ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ እንዲሆን የሚያበረክቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ፤ የመገናኛ ብዙኃኑና ጋዜጠኞች በምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው ለመዘገብ የሚያስችል የፍቃድ ጥያቄያቸውን ለቦርዱ እንዲያቀርቡ ይህንን ጥሪ ማድረግ አስፈልጓል፡፡ በዚህ መሠረት ለመዘገብ ጥያቄ የሚያቀርቡ የመገናኛ ብዙኃን፡

Share this post