Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

የምርጫ ቦርድ የጥሪ ማዕከል አገልግሎት መስጠት ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ባልተካሄደባቸው ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ሶማሌ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና አፋር ክልሎች ቀሪና የድጋሚ ምርጫ ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ለማከናወን በዝግጅት ላይ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም መሰረት ቦርዱ ምርጫ በሚያደርግባቸው አካባቢዎች ለሚፈጠሩ ልዩ ልዩ ሁኔታዎች እና ለመረጃ መለዋወጥ እንዲያገለግል ጊዜያዊ የጥሪ ማዕከል አቋቁማል ስለሆነም ከ6ኛው ዙር ሀገራዊ ቀሪና የድጋሚ ምርጫ ጋር በተያያዘ መረጃ ለማግኘት፤መረጃ ለመስጠት እና አስፈላጊ የሆኑ ጥቆማዎችን ለምርጫ ቦርድ ለማቅረብ የሚከተሉትን ነፃ የስልክ መስመሮች ይጠቀሙ፡

Share this post

የተለማማጅ ሰራተኛ የቅጥር ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሥሩ ለሚገኙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ተለማማጅ ሰራተኞችን /Internship/ ቀጥሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ በዚሁም መሠረት ከዚህ በታቸው የተገለፁትን መስፈርቶች የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ከዚህ በታች በተጠቀሰው የስራ ማመልከቻ ማስፈንጠሪያ በመንካት ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲን በተመለከተ ከቦርዱ የተሰጠ መግለጫ

የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ ሊቀመንበር ከሀገር መውጣታቸውንና ፓርቲውንም የሚመራ ሰው መወከላቸውን ከውጭ ሀገር ሆነው ለቦርዱ ሲያሳውቁ ከፓርቲው አመራሮች መኃል ይህ በሊቀመንበሩ የተሰጠው የውክልና ሥልጣን ደንቡን የተፃረረ ነው የሚል ቅሬታ ለቦርዱ አቀረቡ፡፡ ቦርዱም ሊቀመንበሩ የሰጡት የውክልና ሥልጣን ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ አንፃር የተፈፀመ መሆን አለመሆኑን መረመረ፡፡ የፓርቲው መተዳደያ ደንብ አንቀጽ 22/1/ የፓርቲው ሊቀመንበር በማይኖሩበት ወቅት ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበሩ ሊቀመንበሩን ተክተው እንደሚሰሩ ደንግጓል፡፡ በዚሁ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ከሀገር በወጡት የፓርቲው ሊቀመንበር የተሰጠው ውክልና ደንቡን የተፃረረ በመሆኑ ቦርዱ ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡ በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀጽ 22/1/ መሠረትም እንዲፈፅም ወስኗል፡፡ ይሁንና በፓርቲው አመራሮች መኃል አለመግባባቱ እየጨመረ በመሄዱ በአዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 74 (6) መሠረት ጉዳያቸው በባለሙያዎች ጉባኤ እንዲታይ ቦርዱ ወስኖ የባለሙ

Share this post

የ6ኛው ዙር ቀሪና ድጋሚ ምርጫ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በመስቃንና ማረቆ የምርጫ ክልል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. እንዲሁም መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች ምርጫው ባልተካሄደባቸው እንዲሁም ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸው በአፋር፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ምርጫዎችን ያካሂዳል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በመስቃንና ማረቆ የምርጫ ክልል ለሚደረገው ድጋሚ ምርጫ:

- በቀበሌ 1 ምርጫ ጣቢያ ቆሼ

- በሰሜን ቆሼ ምርጫ ጣቢያ ቁጥር 1

- በቆሼ 02 ምርጫ ጣቢያ ቁጥር 3 እንዲሁም

-በእንሴኖ 01 ምርጫ ጣቢያ ቁጥር 2 የመራጮች ምዝገባ ከሚያዝያ 21 እስከ ግንቦት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ ይከናወናል።

የ6ኛው ዙር ቀሪና ድጋሚ ምርጫ በአፋር ክልል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. እንዲሁም መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች ምርጫው ባልተካሄደባቸው እንዲሁም ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸው በአፋር፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ምርጫዎችን ያካሂዳል።

በአፋር ክልል ለሚካሄደው ምርጫ በዳሎል፥ ጉሊና፥ አዲሌላ፥ ዳሊፋጌ፥ እንዲሁም ዳዌ የምርጫ ክልሎች በሙሉ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ የሚከናወን ሲሆን:

የ6ኛው ዙር ቀሪና ድጋሚ ምርጫ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. እንዲሁም መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ማካሄዱ ይታወቃል። ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች ምርጫው ባልተካሄደባቸው እንዲሁም ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸው በአፋር፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ምርጫዎችን ያካሂዳል።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለሚካሄደው ምርጫ በ ደምቤ፥ ምዥጋ፥ ሰዳል፥ ዛይ፥ ቡለን፥ ዳንጉር፥ ድባጤ፥ ወንበራ፥ ማንዱራ፥ ፓዌ፥ ጉባ፥ እና ልዩ ሽናሻ የምርጫ ክልሎች በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ በሙሉ የሚከናወን ሲሆን ፡

• በመንጌ የምርጫ ክልል፤ በሰላማ ምርጫ ጣቢያ ሰላማ-ሀ

• በሆሞሻ የምርጫ ክልል፤ በ01 ቀበሌ ምርጫ ጣቢያ 01 ቀበሌ 01 ሀ2B

• በአሶሳ ሆሃ ምርጫ ጣቢያ፤ አምባ 7 ምርጫ ጣቢያ አምባ 7

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛዉ ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸዉ የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማእከላዊ ኢትዮጵያ በሚገኙ ምርጫ ክልሎች ምርጫ ለማከናወን የወጣ የምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሰሌዳ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛዉ ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸዉ የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማእከላዊ ኢትዮጵያ በሚገኙ ምርጫ ክልሎች ምርጫ ለማከናወን የወጣ የምርጫ አፈፃፀም የጊዜ ሰሌዳ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫና በድኅረ ምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን በተመለከተ አስጠንቶ ባጠናቀቀው ጥናት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫ እና በድህረ ምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን በተመለከተ አስጠንቶ ባጠናቀቀው ጥናት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር መጋቢት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. ውይይት አካሄደ። ከጥናቱ መጠናቀቅ አስቀድሞ ፤ላለፉት ወራት ጥናቱን መሠረት ያደረጉ ውይይቶች ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ያካሄደ ሲሆን፤ በዚሁ በተጠናቀቀው ጥናት ላይ መጋቢት 12 በተደረገው ውይይት ደግሞ ከዚህ በፊት ያልተሳተፉ ግን የሚመለከታቸው ሲቪል ማኅበራትን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል።

Share this post